በቁጥር (ከመጋቢት 24, 2010 እስከ ሚያዚያ 22, 2013)1 እነዚህ ቁጥሮች የሚያመለክቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደስልጣን ከመጡበት መጋቢት 24, 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገሪቱ የተከሰቱ የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶችን፣ በዚህ ምክንያት የደረሱ የሞት ጉዳቶች፣ እንዲሁም በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ የተቃጡ ጥቃቶችን ነው።
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 1,515
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 7,055
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 3,908
ኢትዮጵያን በተመለከተ በቁጥር የተደገፉ መረጃዎችን እዚህ፣ ሁሉንም የአክሌድ ስራዎች ደግሞ እዚህ ጋር በመጫን ያገኛሉ።
የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ብዙ ሟቾች የተፈጠሩባቸው ክስተቶች የነበሩ ሲሆን በመላው አገሪቱ የመንግሥት ኃይሎች ከመሀል ከተማ ርቀው በሚገኙ አካባቢዎች ላይ የሚንቀሳቀሱ በርካታ የታጠቁ የአመፅ እንቅስቃሴዎችን ለመዋጋት የሚያደርጉት ትግል የአለመረጋጋቱን ቀጣይነት የሚያሳይ ነው፡፡ መንግስት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) – ሸኔ ታጣቂዎችን በጅማ ዞን ፣ በኦሮሚያ ውስጥ ሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ-ዳገም ወረዳ፣ እና ደምቢ ዶሎ ከተማ ውስጥ በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ባልሆኑ ግለሰቦች ላይ ጥቃቶችን አድርሷል ሲል ከሷል። እነዚህ ጥቃቶች ቢያንስ ለ40 ሰዎች ሞት ምክንያት ሆነዋል፡፡ ሚያዚያ 17, 2013 በኦሮሚያ ክልል የፀጥታ አካላት አንድ የዪንቨርስቲ መምህርን ደምቢ ዶሎ በሚገኘው ቤቱ በድንገት በመገኘት ተኩሰው ገድለውታል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሃ.ት.) ጋር ግንኙነት ያላቸው ኃይሎች በዋግ ሀምራ ዞን (አማራ ክልል) በሚገኙ አካባቢዎች ጥቃት በመሰንዘር እስከ 11 ሰዎች መግደላቸው ተዘግቧል።
በትግራይ የቀጠለው አለመረጋጋት በአዲግራት እና አክሱም መካከል ያለውን ዋና መንገድ ለአጭር ጊዜ መዝጋቱን እና ይህንንም ተከትሎ የሰብአዊ እርዳታ ሠራተኞች አቅርቦት በጎንደር በኩል እንዲያደርሱ ተገደዋል። (የተመድ ሰብአዊ ግንኙነቶች ማስተባበሪያ ቢሮ፣ ሚያዚያ 25, 2013).
በሶማሌ ክልል ከምርጫ ጋር የተያያዙ የተቃውሞ ሰልፎች የቀጠሉ ሲሆን ሰልፈኞቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በአፋር እና በሶማሌ ክልሎች ድንበር ላይ ያሉ አከራካሪ ቦታዎች ላይ ያሉ የምርጫ ጣቢያዎችን ለማስወገድ መወሰኑን አውግዘዋል፡፡
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)፣ እና በአብዛኛው በመንግስት ኦነግ-ሸኔ ተብሎ የሚጠራው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) አሁን ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት መጪው ምርጫ እንዲሰረዝ እና በምትኩ ብሔራዊ የውይይት ጉባኤ እንዲካሄድ ጠይቀዋል፡፡ ኦነሰ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ሀሳብ አቅርቧል (ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ Federalist Congress ሚያዚያ 21, 2013; ኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሚያዚያ 20, 2013; አዲስ ስታንዳርድ ሚያዚያ 21, 2013)። የኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በቅርቡ ኦነግ-ሸኔ እና ህ.ወ.ሃ.ት.ን የሽብር ድርጅቶች እንዲባሉ ሀሳብ አፅድቋል (የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ / ቤት፣ ግንቦት 1 2021)፡፡
ወቅታዊ የትግራይ ግጭት ሁኔታ
በትግራይ ክልል ያለው ግጭት የቀጠለ ሲሆን በዚህ ሳምንት በአዲግራት እና በአክሱም መካከል ያለውን ዋና መስመር በመዝጋቱ የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽነትን በጊዜያዊነት ገድቧል (የተመድ ሰብአዊ ግንኙነቶች ማስተባበሪያ ቢሮ፣, ሚያዚያ 25, 2013)። የህወሃት ሀይሎች በአማራ ክልል በዋግ ሀምራ ዞን አካባቢዎች ጥቃት በመሰንዘር 11 ሰዎችን የገደሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ሰዎች ይገኙበታል (ቪኦኤ አማርኛ፣ ሚያዚያ 19, 2013; ይህንን ክስተት በተመለከተ ላለ ዝርዝር ከታች የሚገኘውን ክፍል ይመልከቱ።
ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያም እና ኤርትራ “የኤርትራ ወታደሮችን የአወጣጥ ወታደራዊ ቴክኒኮች” እየተወያዩ መሆኑን ቢገልጽም በቅርቡ የተገኙ ሰነዶች ግን የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ክልል የምግብ እርዳታን እንዳያልፍ እያገዱ እና እየዘረፉ መሆናቸውን ያሳያል (ቢቢሲ አማርኛ፣ ሚያዚያ 19 2013; ፍራንስ24፣ ሚያዚያ 19, 2013)። የኤርትራ መንግሥት ክሱን አስተባብሏል (ቪኦኤ ትግርኛ፣ ሚያዚያ 20, 2013)፡፡ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ምላሹን ለማሻሻል “ተጨማሪ አቅም ፣ ገንዘብ ፣ እንዲሁም ያልተደናቀፈ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ተደራሽነት” ያስፈልጋል ብሏል (የተመድ ዜና፣ ሚያዚያ 21, 2013)።
ክልላዊ ትኩረት: በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል የቀጠለው አለመረጋጋት
ባለፈው ሳምንት በአማራ እና ኦሮምያ ክልሎች የተለያዩ ታጠቂ ቡድኖች በፈፀሙሟቸው ጥቃቶች ምክንያት ከፍተኛ የሞት ቁጥር የተመዘገበባቸው ክስተቶች ተፈጥረው ነበር (ከዚህ በታች ያለውን ቁጥር ይመልከቱ)። በኦሮሚያ ክልል ጥቃቶቹ የተፈጸሙት የኦነግ-ሸኔ ታጣቂዎች እንደሆኑ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ሲሆን በዋናነት ያነጣጠሩት አማራዎች ላይ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በአማራ ክልል ልዩ ሀይል እና በቅማንት እንቅስቃሴ የጎሳ ሚሊሻዎች መካከል የተነሳ ግጭት በርካቶችን ለህልፈት ዳርጏል፣ የፌደራል መንግስትም ጣልቃ እንዲገባ አድርጏል፡፡
በአማራ ክልል ሁለት ኮማንድ ፖስቶች ተቋቁመዋል፡፡ የመጀመሪያው ኮማንድ ፖስት በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሚያ ዞኖች ሚያዚያ 10, 2013 የተቋቋመ ነው (ለበለጠ ዝርዝር ኢፒኦ ሳምንታዊ ከሚያዚያ 2, 2013 እስከ ሚያዚያ 8, 2013 ይመልከቱ)፡፡ ሚያዚያ 21, 2013 በክልሉ ልዩ ኃይል እና የቅማንት ብሄር ጋር ግንኙነት ባላቸው ሚሊሻዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በመአከላዊ ጎንደር ጭልጋ እና ዙሪያውን ባሉ አካባቢዎች ሌላ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ሚያዚያ 21, 2013፣ ለበለጠ ዝርዝር ኢፒኦ ሳምንታዊ ከሚያዚያ 9, 2013 እስከ ሚያዚያ 15, 2013)።
በአማራ ክልል ሚያዚያ 18, 2013 ከህ.ወ.ሃ.ት. ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጥሩ ያላቸው ታጣቂዎች በኒራቅ ከተማ ዋግ ሀምራ ዞን ጥቃት በመፈፀም በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦችን ጨምሮ 11 ሰዎች ገድለዋል (ዋግህምራ ኮምኒኬሽን፣ ሚያዚያ 19, 2013፤ ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 19, 2013)። የህወሃት ምንጮች የመሳሪያ ማከማቻ መቆጣጥራቸውን እና አስፈላጊ ቁሳቁሶች መውሰዳቸውን ቢገልፁም የመንግስት ግንኙነት ግን የአማራ ክልል ልዩ ሀይሎች ጥቃቱን ስኬታማ በሆነ ሁኔታ መከላከላቸውን አስታውቋል (አዲስ ስታንዳርድ, ሚያዚያ 20, 2013)። ህ.ወ.ሃ.ት. ከአንድ ወር በፊት የካቲት 16, 2013 ገደማ ተመሳሳይ ጥቃት በዋግ ሀምራ ዞን ትፀታ አካባቢ አድርሷል (ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 19, 2013)።
በተጨማሪም ሚያዚያ 22 2013 ላይ የሱዳን የጦር ሀይሎች ከኢትዮጵያ ድንበር በ70 ኪሜ ርቀት ላይ ወደሚገኝ መንዶቃ የተባለ ምዕራብ ጎንደር አካባቢ ላይ ወደሚገኝ እርሻ ከፍተኛ መሳሪያዎችን መተኮሳቸው ተዘግቧል (ዲደብሊው አማርኛ ሚያዚያ 22, 2013)። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ አካባቢ ሚሊሻዎች፣ እና ፀረ-ሽምቅ ሀይሎች የወሰዱትን የመከላከል እርምጃ ተከትሎ የሱዳን ሀይሎች ከቦታው አፈግፈገዋል።
በኦሮሚያ ክልል ቢያንስ 40 ግለሰቦች መሞታቸው ተዘግቧል፤ 20 ባለፈው ሳምንት 20 ደግሞ ከዚያ በፊት በነበረው ሳምንት የተከሰቱ ናቸው። ሚያዚያ 15, 2013 የኦነግ-ሸኔ ታጣቂዎች በሊሙ ቆሳ ወረዳ (ጅማ ዞን) በቀጠጮ ቂርቂራ እና ጋሌ ቀበሌዎች በአማራዎች ላይ ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎ የፌደራል እና ክልል ደህንነት ሀይሎች ወደቦታው ገብተዋል። የአካባቢው ሀላፊዎች ቢያንስ 20 በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች መገደላቸውን የጠቀሱ ሲሆን አንድ አንድ ምንጮች ደግሞ የሟቾችን ቁጥር ወደ 29 ከፍ ያደርጋሉ (የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ሚያዚያ 17, 2013; ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 20, 2013; ሬውተርስ፣ ሚያዚያ 22, 2013)። በተጨማሪም ሚያዚያ 20, 2013 ላይ ያልታወቁ ታጣቂዎች ከአዲስ አበባ ወደጎጃም የሚጏዙ የጭነት መኪናዎችን በኩዩ ዳግም ወረዳ ድንበር አካባቢ በሚገኘው የደብረ ጉራቻ ከተማ ላይ በማጥቃት አምስት ሰዎች ገድለዋል። ከሁለት ቀናት በኻላ ከኦነግ-ሸኔ እንደሆኑ የተጠረጠሩ ታጣቂዎች በአሙሩ ቀበሌ (ሆሮ ጉድሩ, ወለጋ ዞን) ከአውቶቡስ ውስጥ ካሰወረዷቸው ውስጥ 15 ሰዎችን ተኩሰው ገድለው በቁጥር ያልታወቁ ሰዎችን ደግሞ አቁስለዋል (የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ሚያዚያ 22, 2013 ሚያዚያ 22፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን፣ ሚያዚያ 22, 2013)።
አንድ ምስክር እንዳለው ከሆነ ታጣቂዎቹ ተጎጂዎችን ኦሮምኛ ባለመናገራቸው እንደለዯቸው ተናግሯል (ቢቢሲ አማርኛ፣ ሚያዚያ 23, 2013)፤ ሆኖም ግን ዘገባዎች ሟቾች ከኦሮሞም ከአማራም ብሄሮች መሆናቸውን ያሳያሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሚያዚያ 22, 2013 በምስራቅ ወለጋ ዞን ሊሞ ጋንዶቲ አሬኩምቤ ወረዳ ሰልፍ የወጡ ግለሰቦች በአካባቢው በአማራዎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ተከትሎ የሚከሰተውን የህይወት እና ንብረት መጥፋት አውግዘዋል (የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ሚያዚያ 22, 2013)።
ከምርጫ ጋር የተያያዙ ክርክሮች እና ግጭቶች
የምርጫውን መቅረብ ተከትሎ የኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች የተለያዩ ከምርጫ ጋር የተያያዙ ክርክሮችን ሲዳኙ የቆዩ ሲሆን በአብዛኛው የምርጫ ቦርድን ውሳኔ ሰርዘዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ገዳ ነፃነት ፓርቲ-ገዳ ቢሊሱማ እና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ሕብረት (ኦዳ ፓርቲ) ከምዝገባ እንዲሰረዙ ያሳለፈውን ውሳኔ ሽሯል (ቢቢሲ አማርኛ፣ ሚያዚያ 20, 2013 28; የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ሕብረት፣ ሚያዚያ 21, 2013)። ሆኖም ግን የእጩዎች ምዝገባ ስለተጠናቀቀ እና የምርጫ ካርዶቹ ህትመት እየተካሄደ በመሆኑ ሁለቱም ወገኖች በምርጫ ካርዶቹ ላይ የሉም ፡፡ ይህንን ተከትሎም የገዳ ቢሊሱማ ፓርቲ ምርጫውን ፍትሃዊ በሆነ ሁኔት ለመዘጋጀት እና ለመሳተፍ ምርጫው በስድስት ወር እንዲራዘም ጠይቋል። በተመሳሳይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከሐረሪ ክልል ውጭ የሚኖሩት ሐረሪዎች የክልሉን ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እንዲመርጡ መከልከሉ አግባብ አይደለም ሲል የምርጫ ቦርድን ውሳኔ ውድቅ አድርጏል (ሪፖርተር፣ ሚያዚያ 20, 2013; ለዝርዝሩ ኢፒኦ ሳምንታዊ ከመጋቢት 25 2013 እስከ ሚያዚያ 1 2013ን ይመልከቱ)።
ከዚህም በተጨማሪ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ውስጥ በክፍያ ዙሪያ የተነሳ ውዝግብን ተከትሎ አንዳንድ የምርጫ ሰራተኞች ሥራ አቁመዋል፡፡ ይህ ደግሞ የመራጮችን ምዝገባ አስተጏጉሏል (ቪኦኤ አማርኛ፣ ሚያዚያ 20, 2013)። በተመሳሳይ ጊዜ የድሬዳዋ አስተዳደር አንዳንድ የምርጫ አስፈፃሚዎች ላይ በከተማው ውስጥ የተወሰኑ ጥቃቶች መድረሳቸውን እና መራጮች እንዳይመዘገቡ ማስፈራሪያ እየደረሳቸው እንደሆነ ገልጿል(ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 20, 2013)። አስተዳደሩ በምርጫ አስፈፃሚዎቹ ጥቃቱን የፈፀሙት እና መራጮችን ያስፈራሩት እንደማን እንደሆኑ ግልፅ አላደረገም፡፡ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ከምዝገባ ጋር የተያያዙ ግጭቶች የተለመዱ ሆነዋል፡፡ የምርጫ ቦርድ በአፋር እና በሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢ ያሉ የሚያከራክሩ ቦታዎች ላይ ያሉ የምርጫ ጣቢያዎችን ለመሰረዝ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የሚካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች በሶማሌ ክልል ቀጥለዋል (ቮስ ቲቪ፣ ሚያዚያ 20, 2013 ሀ፤ ሚያዚያ 20, 2013ለ)፡፡